Afela አፍላ
አፍላ ለፈጣን መረጀጃ
''ኢስላም ለፈጣሪ እጅን መስጠት እና በትእዛዙ ማደር ማለት ሲሆን
አምልኮትን ሁሉ በብቸኝነት ፍጹም ለአላህ ማድረግ ። ሌሎችን ፍጡራን የስልጣኑ ተጋሪ አለማድረግ፡ ይህን ዩኒቨረስ
ብቻውን የፈጠረለፍጡራን ሁሉ ሲሳያቸውን እሱ ብቻውን የሚመግብለስልጣኑ ተጋሪ ወይም እረዳት ተባባሪ የሌለው
ሃያል ጌታ መሆኑን ማመን። ነገ የትንሳኤ ቀን የፍርዱ ቀን ብቸኛ ባለቤት አላህ መሆኑን ማመን። ይህን ይመስላል
ብለን የምንመስልበት አምሳያ የሌለው ሃያል አምላክ አላህ በመባል ይታወቃል።
ኢስላም ማለት ለአላህ በመመሪያው በማደር ለትእዛዞቹ መንበርከክ ፡ እምነትን እና ልቦናን ለአላህ ፍጹም ማድረግ እና
ከአላህ ዘንድ የመጡ መመሪያዎችን በፍጹምነት ማ
04/11/2025
Visit TikTok to discover videos! Watch, follow, and discover more trending content.
28/10/2025
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-
👉 ኢትዮጵያ ትልቁ የምታወጣው ወጪ ለማዳበሪያ እና ነዳጅ ነው፤
👉 ዳንጎቴ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚያለማው የማዳበሪያ ፋብሪካ 30 ሚሊየን ኩንታል ዩሪያ የሚያመርት ነው፣
👉 ቢሾፍቱ የሚሰራው አየር መንገድ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያመጣል፤ አየር መንገዱ ከ100 ሚሊየን በላይ ተጓዦችን በዓመት የሚያስተናግድ በመሆኑ ከአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ ይሆናል፣
👉 እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የቤት ባለቤት እንዲሆን ማድረግ የሚቻል አይደለም፤ ቢያንስ ሁሉም ሰው የኪራይ ቤት እንዳያጣ ማድረግ ያስፈልጋል፣
👉 የኮሪደር ልማት ዋና ዓላማው ያለንን ቦታ በአግባቡ እንድንጠቀም የሚያደርግ ነው፤ የኮሪደር ልማት የፈጠራ አቅም እና የኑሮ ዘዬን የቀየረ ነው፣
👉 አዲስ አበባ ውስጥ ከአንድ ሺህ በላይ ትንንሽ ስታዲየሞች ተገንብተዋል፤ የተገነቡት ትንንሽ ስታዲየሞች በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጥሩ ተጫዋቾችን ያበረክታሉ።
የቀይ ባሕር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልካዓ ምድራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን!! p.m Dr Abiy @
26/10/2025
''ቀይ ባህር ያስፈልገናል'' በ2ሚሊዮን ህዝብ መታፈን የለብንም። ''ፊልድ ማርሻል ብረሃኑ ጁላ''
ፈልድ ማርሻሉ በ118ተኛው የሰራዊት ቀን ሲከበር ባስተላለፊት መልዕክት ''ቀይ ባህር ያስፈልገናል'' የኢትዮጵያ ሕዝብ ከ10 አመት በሗላ 200 ሚሊዮን መሆኑ አይቀርም፤ እናም 200 ሚሊዮን ህዝብ በ2 ሚሊዮን ህዝብ መታፈን የለበትም በማለት ጠቆም አድርገው አልፈዋል።
አክለውም ኢትዮጵያ ሦስት ነገር ያስፈልጋታል፤ ሰላም፣ ልማትና የባሕር በር" በማለት በቦሌም በባሌም ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት ትሆናለች ብለዋል።
የፊልድ ማርሻሉን ሃሳብ እንደት ያዩታል?
26/10/2025
በጃፓን ጦርነት ወቅት የወንድሙን ሬሳ አስክሬን በጀርባው አዝሎ በጥልቅ ስሜት ሊቀብር ይሄድ የነበረውን ታዳጊ ሕጻን ያስተዋለ አንድ ወታደር!
ለምን እራስህን ታደክማለህ የሕጻኑን እሬሳ ጥለኸው ብትሄድ እኮ ድካምህ
ይቀንስልህ አልነበር? ሲል ጠየቀው።
ሕጻኑም ሲመልስ እንዲህ አለ ወንድሜ ነው እኔን አይከብደኝም አለው
ያን ጌዜ ጥያቄውን ያቀረበው ወታደር ራሱን መቆጣጠር አልቻለም ..... ስሜቱ በጣም ተነካ ዓይኖቺ በዕንባ ታጠቦ።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በጃፓን ይህ ምስል የወንድማማችነት የአንድነት ተምሳሌት ሆነ
እናም ..... የሕይወት መርሃችን እንዲህ ቢሆንስ
ወንድሜ ነው እኔን አይከብደኝም!
እህቴ ናት እኔን አትከብደኝም!
ወንድምህ ቢወድቅ አንሳው!
እህትህ ብትደክም ከጉኗ ቁም!
ወንድምህ ቢስት በየዋህነት መንፈስ አቅናው!
እህትህ ስህተት ብትሰራ ይቅርታህን አትንፈጋት።
ለሁሉም ሙስሊም ኡማ:- ሰሞኑን በየ ሶሻል ሚዲያው የሚሰራጩ የውስጥ ጉዳዬችን ወደ አደባባይ የማውጣት እና ኡማውን ለሁለት የመሰንጠቅ አዝማሚያ ያላቸው መልዕክቶች መሰራጨታቸው በፍጥነት ይታረሙ።
በሙፍቲ ህልፈት ብናዝንም ከቀደምት ሰለፎች የትዕግስት ቀንዲል ትምህርት ልንወስድ ይገባል ። ነብያችን(ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባረፉ ወቅት የነበረዉን ክስተት መለስ ብለን ማስታወሱ ብርታትን ይቸረናል ።
ነብያችን (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሲያልፉ ብዙዎቹ ድንጋጤ ዉስጥ ገብተው ነበር። ከፊሎቹ አልሞቱም ብለዉ እስከ መሞገት ደርሰዋል ። የተቀሩት ደግሞ እግራቸው ለመቆም ምላሳቸው ለመናገር አቅም ገደደው።
ህልፈተ ዜናው የደረሳቸዉ አቡበክር ሲዲቅ ከእናታችን አዒሻ ቤት ገብተዉ ያንን በሻሻ ፊት ደጋግመው ሳሙት ። ከዚያዉ ወደ መስጂድ አመሩ ። ሰይድ ዑመር ከመስጂድ ዉስጥ እየተናገሩ ሳለ አቡበክር መናገር ጀመሩ ። የመስጂዱ ታዳሚ ትኩረቱን ወደ አቡበክር ሲዲቅ አዞረ። አቡበክር ሲዲቅም እንዲህ ሲሉ ተናገሩ ፤
"من كان يعبد محمدا فإن محمدا قد مات ومن كان يعبد الله فإن الله حي لا يموت."
"ሙሐመድን የሚያመልክ ሰው ካለ መሐመድ በርግጥ ሞተዋል ። አላህን የሚያመልክ ሰው ግን አላህ ህያው ነው አይሞትም።
አስከትለዉም እንዲህ የሚለዉን የቁርዐን አያት አነበቡ ፡
وَمَا مُحَمَّدٌ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ ۚ أَفَإِن مَّاتَ أَوْ قُتِلَ انقَلَبْتُمْ عَلَىٰ أَعْقَابِكُمْ ۚ وَمَن يَنقَلِبْ عَلَىٰ عَقِبَيْهِ فَلَن يَضُرَّ اللَّهَ شَيْئًا ۗ وَسَيَجْزِي اللَّهُ الشَّاكِرِينَ
“ሙሐመድም ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ ታዲያ ቢሞት ወይም ቢገደል ወደ ኋላችሁ ትገለበጣላችሁን ወደኋላው የሚገለበጥም ሰው አላህን ምንም አይጎዳም፡፡ አላህም አመስጋኞቹን በእርግጥ ይመነዳል፡፡”
ይህንን የአቡበክር ሲዲቅ ንግግርን የሰሙ በሙሉ በነብያችን(ሶለለሁ ዐለይሂ ወሰለም) ህልፈት እርግጠኛ ሆኑ ። ይህንን የቁርዐን አያት ከአሁን በፊት ያልሰሙት እስከሚመስላቸዉ ድረስ በአዲስ ተቀባበሉት ።
እኛም በአቋማችን የፀናን ሆነን ሞትን ልንጠብቀው ይገባል። የሙፍቲያችን ከዱንያ መሻገር ለእርስዎ እረፍት ቢሆንም ትልቅ ክፍተት እንደሚፈጥር እሙን ነው። ቢሆንም ግን “እኔ አንድ ዑመር ብሔድ አሏህ ብዙ ዑመሮች አሉት” የሚለዉን ዘመን ተሻጋሪ ንንግራቸዉን መዘንጋት የለብንም ። አዎን አሏህ ብዙ ዑመሮች አሉት ። በሸይኻችን ማለፍ ክፍተት ይኖራል ብላቹ ላሰባችሁ በሙሉ የተጀመሩ የፅናት ጉዞዎች እንደማይደናቀፉ በአሏህ ስም ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
አባታችንን ሐጂ ዑመር ላይመለሱ ተሸኝተዋል ። አስተምህሮታቸዉን ማስቀጠል የጋራ ሓላፊነታችን ሆኗል። ሙፍቲ በዘመናቸዉ ከጣፋጭ የሐሪማ ኑረት እስከ አሳማሚ ግፍ ያካተተን የህይወት ዉጣ ዉረድን አስተናግደዋል ። ያለፉት ጥቂት አመታት ደስታን አልሰጧቸዉም ነበር ። “ዉስጣችን ነዷል እስኪ ሁላችንንም አሏህ ያሽረን” በሚለው ቃል አሏህን እስከመማፀን ደርሰዋል።
በጣም የሚያሳዝነው በህይወት ሳሉ ክብራቸውን የተጋፉ በእለት ሕልፈታቸው እንኳን አላረፉም። ሐገር የሀዘን ማቅ ተከናንቦ ባለበት ሁኔታ አብረዉ ማዘን ባይችሉ እንኳን ከክፋት አለመታቀባቸው መጪዉን ጊዜ በመልካም ለመገመት ያዳግታል ። በርግጥ ለዚህ ያበቃቸው ብልሹ አስተምህሮት በሌሎች ሐገራት ምን እያደረገ እንደሆነ ሁሉም ያዉቃል። እንዲህ ያሉ ከእምነትም ሆነ ከባህል ያፈነገጡ ብልሹ ምግባሮችን በጊዜ መከርከምና ማረቅ የሁሉም ኢትዮጲያዊ የጋራ ሐላፊነት ነው።
በስተመጨረሻም ለመላዉ የሙፍቲ ወዳጆች ሶብሩን ለሙፍቲ ደግሞ ጀነትን
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Telephone
Website
Address
Kara Korie
Addis Ababa
ADDISABEBA

01/11/2025